የይሖዋ ምስክሮች የደም መቀበል ህክምና (Blood transfusion) ክልከላ የአምላክን ትዕዛዝ
ለማክበር ነው ወይስ ሌላ አላማ አለው? ይህን ጽሑፍ በጥሞና በማንበብ ወገንን ከሞት ያድኑ፡፡
የይሐዋ ምስክሮች እስከ 1927 ደም መብላትን የሚከለክለው የመጽሓፍ ቅዱስ ህግ ለክርስቲያኖች አይደለም
ብለው ያስተምሩ ነር፡፡ በመጠበቂያ ግንብ መጽሄታቸው ኖቬምበር 15፣1892፣ገጽ 350-351 ላይ እና ኤፕሪል 15፣1909፣ገጽ
116-117 ላይ የደም መብላት ክልከላው ህግ ለአይሁዶች ብቻ እንደሆነ እና በአዲስኪዳን ያለውን ሀሳብ ክርስቲያኖች ለአይሁድ
እና ለአረማዊያን መሰናከያ እንደይሆኑ እና ለቤክርስቲያን ሰላም ነበር ይላሉ፡፡
በመጠበቂያ ግንብ መጽሄታቸው 1927 ዲሴምበር 15፣ገጽ 371 ላይ ነው ለመጀመሪ ጊዜ ነው የይሖዋ
ምስክሮች ድርጅት የቀድሞ ሐሳቡን በመቀያር አምላክ ከኖህ ጋር የገባው ቃልኪዳን ለሰው ዘር ሁሉ ይሆናል በማለት ለመጀመሪ ጊዜ
የደም መብላት ክልከላውን ያደረጉት፡፡
No comments:
Post a Comment