ብኩርና ሁለት ትርጉም ኣለዉ፡፡ኣንደኛዉ ቀድሞ የተወለደ ማለት ነዉ፡፡ሁለተኛዉ ስልጣን አለቅነት ነዉ፡፡የመጀመሪያዉ ብኩርና (ቀድሞ መወለድ) ለሌላ ወገን ሊተላለፍ አይችልም፡፡የሁለተኛዉ ብኩርን (የበላይነት/ስልጣን) ለሌላ ወገን ሊተላለፍ ይችላል፡፡ብኩርና ስልጣን ስለመሆኑ የያዕቆብን እና የኤሳዉን ታሪክ ማየት ይቻላል፡፡31፤ ያዕቆብም። በመጀመሪያ ብኵርናህን ሽጥልኝ አለው። 32፤ ዔሳውም። እነሆ፥ እኔ ልሞት ነኝ፤ ይህች ብኵርና ለምኔ ናት? አለ ። 33፤ ያዕቆብም። እስኪ በመጀመሪያ ማልልኝ አለው። ማለለትም፤ ብኵርናውንም ለያዕቆብ ሸጠ። ዘፍ 25፡31-33 ታዲያ ያዕቆብ ከኤሳዉ በእድሜ በለጠ?በፍጹም፡፡ነገር ግን በስልጣን በለጠ፡፡
ታዲያ እየሱ ለምን የፍጥረታት በኩር ተባለ? በአማርኛ ምክንያትን ስለሆነ ወይም ኣልና ብለን ስንገልጽ በእንግሊዝኛ because/For/Therefore እያልን እንገልጻለን፡፡ግሪኩም hoti ይለዋል፡፡ቆላ 1፡16 እየሱስ ለምን የፍጥረታት ሁሉ በኩር እንደተባለ በዚሁ መልክ ይገልጻል፡፡
የሚታዩትና የማይታዩትም፥ ዙፋናት ቢሆኑ ወይም ጌትነት ወይም አለቅነት ወይም ሥልጣናት፥ በሰማይና በምድር ያሉት ሁሉ በእርሱ ተፈጥረዋልና
For by Him all things were created, both in the heavens and on earth, visible and invisible, whether thrones or dominions or rulers or authorities-- all things have been created through Him and for Him.
ότι(hoti) for εν in αυτώ
him εκτίσθη
were created τα πάντα the whole(all),τα
the things εν
in τοις
the ουρανοίς heavens, και
and τα
the things επί
upon της
the γης
earth–τα
the ορατά
visible καιand τα the
αόρατα unseen;
είτε whether
θρόνοι thrones,
είτε whether
κυριότητες lordships,
είτε whether
αρχαί sovereignties,
είτε whether
εξουσίαι authorities;
ταπάντα the
whole(all) δι΄ through
αυτού him
και and
εις in
αυτόν him
έκτισται have
been created
የፍጥረታት በኩር የተባለዉ ቀድሞ ስለተፈጠረ ቢሆንማ ኖሮ እዚያዉ ሁሉም በእርሱና ለእርሱ ተፈጠሩ ባላለ ነበር፡፡ስለዚህ እየሱስ የፍጥረታት ሁሉ በኩር የተባለዉ በፍጥረታት ላይ ባለዉ ስልጣን ነዉ፡፡ ይህንንም በግልጽ በምክንያት ተጽፎ ከላይ አይተናል፡፡
የይሖዋ ምስክሮች በዚህ የመጽሃፍ ቅዱስ ክፍል በግሪኩ መጽሃፍ ቅዱስ ዉስጥ የሌላ ” ሌሎች” የሚል ቃል ጨምረዋል፡፡ትምህርታቸዉ መጽሃፍ ቅዱስ ዉስጥ ካለ በመጽሃፍ ቅዱስ ዉስጥ የሌለ እና ትርጉሙን የሚቀይር ቃል ማስገባት ለምን አስፈለገ?
No comments:
Post a Comment